ጸጋንና ምህረትን ከጌታ የተቀበልን፣ በምህረቱ ውስጥ ያለን አማኞች ሁሉ፣ ልንኖር የሚጠበቅብን፣ ምህረትን እንዳገኘ ሰው ነው። ምህረትን ያገኘ ሰው ደግሞ፣ አይዝም፣ አይቆጥርም ደግሞም አይፈርድም። ነገርን ከእግዚአብሔር ጋር ብናያያዝ በምህረት እየኖርን ነው፣ ነገርን ከስው ጋር ብናያያዝ ግን በምህረት እየኖረን አይደለም፣ ሰይጣን ከህይወት መንገድ እያወጣን ነው። በክርስቶስ ምህረትን ያገኘን ሁላችን ዛሬ ህይወታችንና አኗኗራችን ማንን ይመስላል? የሚጠሉንን እየወደድን፣ የሚረግሙንን እየመረቅን፣ ? ለሚያሳድዱን እየጸለይን፣ በክፉውስ ፋንታ፣ መልካምን እያደረግን ነው?
view more