በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጌዴዎን የተባለ ስው ምድያማውያንን ፈርቶ በተሸሸገበት ስፍራ፣ የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦለት አንተ ጽኑዕ ኃያል ሰው፥ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው አለው። ጌዴዎን የነበረበት ሁኔታና መልአኩ ተገልጦ የነገረው ቃል በፍጹም አብሮ የሚሄድ አልነበረም። ነገር ግን እግዚአብሔር ሁልጊዜ ከህዝቡ ጋር ነው። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የመሆኑ መለኪያው የምናልፍበት ጊዚያዊ ሁኔታ ሳይሆን፣ የነገረን ቃሉ ነው። እስከ አለም ፍጻሜ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ ስላለን፣ በምናልፍበት በማናቸውም ሁኔታ፣ በክርስቶስ እየሱስ ያገኘነውን አብሮነት እያጣጣምን ልንኖር ይገባናል።
view more