እግዚአብሔርን ማንም አላየውም ነገር ግን አንድያ ልጁ ተረከው አንደሚል ቃሉ፣ እግዚአብሔርን በሚገባ የገለጠው ጌታ እየሱስ ነው። እንዲሁም ሐዋርያቱ አብረው ከጌታ ጋር ስለነበሩ ያዩትንና ከእርሱ የሰሙትን መስክረዋል። በዚህ ክፍል እኛም በክርስቶስ የሆንን የባህርይው ተካፍዮች ከሆንን ምስክሮቹ እንደሆንን እንማራለን።
ይህም እግዚአብሔር ብርሀን እንደሆነ ጨለማም በእርሱ ዘንድ እንደሌለ ፤እኛም በብርሀን ልንመላለስ እንደሚገባንና ደግሞም ጨለማ በእኛ ዘንድ ካለ ንሰሀ መግባትና መመለስ እንዳለብን እንጂ በዚህ ዘመን እንደሚያስተምሩት በስጋ የሚደረግ ሀጢያት ምንም አይደለም ብለን እንዳንጠፋ ያስጠነቅቀናል።
view more