የተወደደ ቀን እንዳለ ሁሉ የክፉ ቀንም እንዳለ ልንገነዘብ ያስፈልጋል። በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንደሆነ ፣እንደማይተወን ፣ያለ እርሱ ፈቃድ በህይወታችን ምንም እንደማያገኝን ልናውቅና ልንረዳ ያስፈልጋል። በስይጣን ሽንገላ እንዳንታለል አዕምሮእችንን ልንጠብቅ ይገባናል። የመጀመሪያና ትልቁ ነገር በዚህ እውነት ውስጥ ሆነን ምሽጋችንን መጠበቅ ነው። በዚህ እውነት ከቆምን ውጊያው የጌታ ስለሚሆን አሸናፊዎች ነን። ይህንን እውነት ጥለን ግን አዎ፣ ጥሎኛል፣ትቶኛል፤ ከእኔ ጋር የለም ካልን በሰይጣን ውሸትና ሽንገላ ተታለን እንወድቃለን።ሰይጣን ሸንጋይና ውሸታም ነው።
view more