መንፈስ ቅዱስ በሙላት የሚሰራብን እራሳችንን የሰጠነውንና የተጠማነውን ያህል ነው፣ የሰዎች ቋንቋ የተደበላለቀው ለክፉ ስራ ስለተባበሩ ሲሆን ይህንን የተለያየውን ቋንቋ ወደ አንድነት መንፈስ ለማምጣት ጌታ ለቤተ ክርስቲያን ይህንን የልሳን ስጦታ ሰጠ፣ ይህ ልሳን በእግዚአብሔር ቃል ላይ የተመሰረተ እውነት ለመሆኑ ምስክር አንዲሆን ሰው በሚሰማውና በሚረዳው ቋንቋ ይነገራል፣ አማኝ ከእግዚአብሔር ጋር የሚነጋገርበት የሚስጥር ቋንቋ ነው ደግሞም በሌሎች ሰዎች የሚተረጎምና ራሳችንን የምናንጽበት ነው፣ ይሀን ልሳን ለመቀበል ሰው ወደ እምነት መምጣት አለበት፣
view more