እግዚአብሔር የሚሰራው በጊዜ ውስጥ ነው፣ መንፈሳዊነት ደግሞ ከእግዚአብሔር ጊዜ ጋር መራመድና ጊዜውን ማስተዋል ነው፣ ለእያንዳንዱ ነገር ተወስኖ የተሰጠ ጊዜ አለ፣ ሁሉም ከጊዜው አያልፍም፣ ሁሉ በጊዜ የተወሰነ ነው፣ ሰው ግን በራሱ ጉዳይ ሲያዝ ዘመንን ለመዋጀት የእግዚአብሔርን ነገር የሚሰማበት ጆሮ የለውም፣ ጊዜን የሚሰማ ጆሮ ደግሞ ከሌለን የጊዜው ጸሎት የለንም የጊዜው ጸሎት ከሌለን ደግሞ የጊዜው መልስ የለንም፣ ከእግዚአብሔር ጊዜ ጋር ስንራመድ ጠቃሚዎች ለዘመኑ መልስና ለእግዚአብሔርም መልክተኞች እንሆናለን፣
view more