አሸናፊ ሕይወት እንድንኖር የሚረዳንና መንፈሳዊ ሰው የሚያስብለን እግዚአብሔር ያየውን ስናይና ያወቀልንን ስናውቅ ነው፣እግዚአብሔር ያየውን ካየን በዙሪያችን ያለ ማንኛውም ሁኔታ አያናውጠንም፣ እርሱ ያየውን ካላየን ግን ከእምነታችን እንጎድላለን ተስፋችን የሆነው እየሱስ ይደበዝዝና በምናየውና በምንሰማው እውነት ባልሆነው ሁሉ የምንናወጥ፣ ጭንቀትንና ፍርሃትን ብቻ የምናስተናግድ እንሆናለን፣ እግዚአብሔር ግን ለአምላክነቱ እውቅናን እየሰጠን ቃሉን ተደግፈን በአረፍት እንድንኖር ይፈልጋል፣
view more