እግዚአብሔር አንዳንድ ጊዜ የስው ልጆችን ለልባቸው ፈቃድ ይሰጣል። ሰው ደግሞ ለልቡ ፈቃድ ሲሰጥ፣ ክንዱን አምላክ ያደርጋል፣ ስለሚፈልገው ነገር የሚያደርገው ሁሉ ትክክል ይመስለዋል፣ የመጨረሻ ጥበቡንና ብርታቱን ይገልጣል ነገር ግን ሰው የእግዚአብሔርን ፅድቅና ዕውነት ማዛባት ሲጀምር፣ ፃድቁና ፍርድ አደላዳዩ አምላክ እግዚአብሔር ይነሳል፣ ጣልቃ ይገባል። እግዚአብሔር ሲነሳ ደግሞ የሰው ኩራትና ትእቢት ሁሉ ከንቱ ይሆናል፣ ትልቅ ነኝ ያለው ትንሽ ይሆናል።
view more